አሞራ
ከWikipedia
አሞራ ጥምብ አንሣ ወይም መንገድ ጠራጊ ወፍ በተለይ የአውሬ በድን የሚበላ ነው። አሞራዎች በማናቸውም አህጉር ላይ ሲገኙ በአንታርክቲካ ወይም በፓሲፊክ ደሴቶች ላይ ግን አይገኙም።
ከአሞሮች ብዙዎቹ ከላባ መላጣ የሆነ ራስ ይኖራቸዋል። ምክንያቱ ባለ-ላባ ራስ በየጊዜ በደም ተቀብቶ ለማጽዳት ያስቸግረው ስለ ነበር ሳይሆን አይቀርም። ከዚያ በላይ በወንዝ ውስጥ በቀላሉ ለማጽዳት ያስችለዋል።
አሞራዎች በ2 ክፍሎች ይገኛሉ። በአፍሪካ በእስያና በአውሮፓ የሚገኘው ወገን ደግሞ ጭላትና ንሥር ይከትታል። በድን ለማግኘት የሚቻላቸው በማየት ብቻ ነው።
በአዲስ አለም (አሜሪካዎች) የሚገኙት አሞሮች ሌላ ወገን ናቸው። እነሱ መብል የሚያገኙ በማሽተት ነው።