መለስ ዜናዊ
ከWikipedia
መለሰ ዜናዊ (የትውልድ ስማቸው ለገሠ ዜናዊ አስረስ) ኢትዮጵያ የፖለቲካ ሰው ናቸው። በአድዋ ትግራይ በ(ሚያዝያ 30 ቀን 1947 ዓ.ም. ተወለዱ። ከ1987 አንስተው በኢትዮጵያ የጠቅላይ ሚኒስትር ሥልጣን በከፍተኛው የአመራር ቦታ ላይ ናቸው። የኢህአዴግና የሕውሓት ፕሬዚዳንት በመሆን ኢህአዴግ ስልጣን ላይ ከወጣ ጀምሮ ይታወቃሉ።
ኣቶ መለስ ዜናዊ ኣባታቸው የትግራይ ተወላጅ ሲሆኑ በእናታቸው በኩል ደግሞ ኤርትራዊ ናቸው፡፡
ይዞታ |
[ለማስተካከል] ወደ ስልጣን አመጣጥ
ሕውሓት የኮሎኔል መንግስቱ ኅይለ ማርያምን አምባ ገነናዊ መንግስት በትጥቅ ሲታገሉ ከነበሩ ድርጅቶች አንዱ ነው። አቶ መለስ የሕወሓት አመራር ኮሚቴ መሪ ሆነው በ1971 ተመረጡ ቀጥሎም በ1975 የዋናው መሪዎች ቡድን አለቃ ሆኑ። የደርግ መንግስት ከወደቀም ጀምሮ የሕውሓትና የኢህአዴግ ሊቀ መንበርም ናቸው። ኢህአዴግ የአራቱ ፖለቲካ ፓርቲዎች ማለትም የኦሮሞ፣ የአማራ፣ የትግራይና የደቡብ ሀዝቦች ብሔር ውህደት ነው። ወደ ስልጣን ሲመጡ በጊዜው ላቋቋሙት ጊዜያዊ መንግስት ፕረዚዳንት ሆነው ካገለገሉ በሗላ 1985 ለመጀመሪያ ጊዜ ጠቅላይ ሚንስትር ሆነው ተመረጡ። በጊዜው የፕረዚደንትነቱን ቦታ የተረከቡት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ናችው። በመቀጠልም አቶ መለስ ከባድ ውዝግብ ባስነሳው የ1997 ግንቦት ምርጫ አሸናፊ ሆነው ለሁለተኛ ጊዜ በስልጣን ላይ ይገኛሉ።
[ለማስተካከል] የኢህአዴግ ደጋፊዎች
በአምባ ገነኑ ደርግ ስር ተጨቁኖ ለነበረው ድሃ ኢትዮጵያዊ የኢህአደግ ወደ ስልጣን መምጣት ከ«የምስራች» ውጭ ሌላ ነገር አልነበረም። ከዚህም የተነሳ ኢህአዴግ ይህ ነው የተባለ ተቃውሞ አልገጠመውም። ከዚህም በተጨማሪ የአረብና የምዕራባውያን መንግስታት ከጎንህ አለን በማለት በብዙ ትግል ስልጣን የተቆናጠጠውን ኢህአደግን በሁለት እግሩ አንዲቆም አስችለውታል።
[ለማስተካከል] የኢህአዴግ ተቃዋሚዎች
ምንም እንኳ በደርግ የግፍ አገዛዝ የተማረረው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ኢህአዴግን ለመቀበልና አብሮ ለመስራት ወደ ኋላ ባይልም ውሎ ሲያድር ግን በኢህአዴግ የአገር ውስጥ ፖሊሲ መከፋቱ አልቀረም። የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ብሎ ራሱን የስየመው ቡድን ከኢህአዴግ ጋር በመቃቃሩ ራሱን ከፓርላማውና ከካቢኔው አግልሎ ወደ ትጥቅ ትግሉ ተመለሰ።
ጠ/ሚ መለስ የኤርትራን የመገንጠል ጥያቄ ያለምንም ማንገራገር መፍቀዳቸው ብቻ ሳይሆን ሁሉም ብሄረሰብ እንዲገነጠል የሚያስችለውን አንቀጽ በህገ መንግስታቸው በማካተታቸው በተለይ በምሁራን ዘንድ የከረረ ተቃውሞ አስነስቶባቸዋል። ሁሉም በክልሉ በቋንቋው ይማር የተሰኘው ፖሊሲያችውም በብዙዎች ዘንድ ጥርጣሬና መከፋፈልን በመፍጠሩ በሀገርና ከሀገር ውጭ በተደጋጋሚ የተቃውሞ ሰልፎች ተካይዶባቸዋል።
በ1997 አጋማሽ ጠቅላላ ምርጫ ሲደረግ ከተለያዩ የፖለቲካ ህቡዕ ፓርቲዎች የተውጣጣ ቅንጅት የተሰኘ ጥምር የፖለቲካ ፓርቲ እንደ አንድ የፖለቲካ ድርጅት ተወዳደረ። በውጤቱም የዓለም ታዛቢዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ከተማ ከመቶ 97 እጁ መራጭ የተቃዋሚውን ፓርቲ ቅንጅትን መረጠ። በውጤቱ የተደናገጠው የአቶ መለስ መንግስት ለመጀመሪያ ጊዜ የአዲስ አበባን ፖሊስ በፌዴራል ቁጥጥር ስር አዞረ። የአዲስ አበባ ምክር ቤትንም በኦሮሚያ መስተዳደር ስር እንዲተዳደር አዲስ ድንጋጌ አወጣ።
ይሁን እንጂ ብዙም ገለልተኛ ታዛቢ በለለበት ከአዲስ አበባ ውጪ ኢሕአዴግ 90 በመቶ ማሸነፉ ስለታወጀ ተቃዋሚዎች አድልዎ ተደርጎብናልና ምርጫው እንደገና ይጣራ ብለው ለከፍተኛ ፍርድ ቤት የይግባኝ ማመልከቻ በማስግባታቸው ማጣርያ ተካሄደ። ተቃዎሚዎች በጠቅላላው የምርጫ ውጤት ባለመስማማታቸው ያሸነፉበትን የፓርላማ ወንበር ባለመቀበል የገዢው ፓርቲ በበላይነት ከተቆጣጠረው ፓርላማ ራሳቸውን አገለሉ።
ሚሥስ አና ጎሜዝ የተባሉ የአውሮፓ ታዛቢ ቡድን መሪ ምርጫው አድልዎና ጫና እንደነበረበት ለዓለም ሕዝብ ምስክርነታቸውን ተናገሩ። አብዛኛዎቹ ታዛቢዎች (አፍሪካ ህብረት አና ጂሚ ካርተር ምርጫው በኢትዮጲያ ከተካሄዱ ምርጫዎች በጣም የተሳለ መሆኑን መሰከሩ) በሺ የሚቆጠር የቅንጅት ደጋፊዎች በዋና ዋና ከተማ በመውጣት ሰላማዊ ሰልፍ በቁጣ በሚገልጽበት ጊዜ ቁጥሩ በርካታ የሆነ ሕዝብ በፖሊስ በቀጥታ በተተኮሰ ጥይት ሕይወቱን አጥቶአል። የአቶ መለስ መንግስት አብዛኛዎችን በህዝብ የተመረጡ የቅንጅት ፓርቲ አባላትንና በሺ የሚቆጠሩ አባላትን ባገር ክህደት አና መንግስትን ለመገልበጥ በመሞከር ከሰሳቸው። 2 ዓመት በፈጀ የፍርድ ሂደትም ፍርድ ቤቱ የቅንጅት መሪዎችን አገርን በመክዳት ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው አገኛቸው ። ይሁን እንጂ ሁሉም የ ቅንጅት መሪዎችና አብዛኛው ደጋፊ አባላት ጥፋታቸውን አምነው ይቅርታ በመጠየቃቸው ከእስር ነጻ ወጡ።
[ለማስተካከል] የሽግግር መንግስታቸው
የመንግስቱ ኃይለ ማርያምን መሸነፍ ተከትሎ የሐምሌው ስምምነት ተደረገ። ይህም ብዙ ብሔር የተሳተፈበትና ቀድሞ ያልታየ ነበር። ይሁን እንጂ ኢህአዴግ ብቻ ጎልቶ የታየበት ስለነበር ብዙኅኑን ያስደሰተ አልነበረም ስለሆነም ከትችትና ከተቃውሞ አላመለጠም።
|
|
---|---|
ንጉሠ ነገስት መንግሥት (1934-1966) | መኮንን እንዳልካቸው · አበበ አረጋይ · አክሊሉ ሀብተ-ወልድ · እንዳልካቸው መኮንን · ሚካኤል እምሩ |
ደርግ (1966-1979) | (ማዕረጉ ተሠረዘ) |
የኢት. ሕዝባዊ ዲሞ. ሪፐብሊክ (1979-1983) | ፍቅረ ሥላሴ ወግደረስ · ሃይሉ ይመኑ* · ተስፋዬ ድንካ* |
የኢት. ፌዴራላዊ ዲሞ. ሪፐብሊክ (1983-አሁን) | ታምራት ላይነህ* · መለስ ዜናዊ |
*ተግባራዊ
|