የኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር

ከWikipedia

የኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠርኢትዮጵያ (እንዲሁም በኤርትራ አብያተ ክርስትያናት) ዋና ካሌንደር ነው። አዲስ ዓመት በጁሊያን ካሌንደር አቆጣጠር በኦገስት 29 ወይም 30 የሚጀምር ሲሆን በግሪጎሪያን ካሌንደር ደግሞ ከ1901 እ.ኤ.አ. እስከ 2099 እ.ኤ.አ. ድረስ በሴፕቴምበር 11 ወይም 12 ይጀምራል። በየአራት ዓመቱ አንድ ቀን ይጨመራል። በአንድ ዓመት ውስጥ አስራ-ሁለት ባለሠላሣ ቀናት እና አንድ ባለ አምስት (ስድስት በአራት ዓመት) ቀናት ያሉባቸው ወራት አሉ።

የአመተ ምህረት ዘመናት ከጎርጎርዮስ 'አኖ ዶሚኒ' በ7 ወይም 8 አመታት የሚለይበት ምክንያት፣ ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት 400 አመት ያህል በኋላ አኒያኖስ እስክንድራዊ ዘመኑን ሲቆጥረው ትስብዕቱ በመጋቢት 29 1 ዓ.ም. እንደ ሆነ ስለ ገመተ ይህ በትስብዕት ዘመን 1ኛ አመት ሆኗል። ይህ አቆጣጠር በምሥራቅ ክርስቲያን አገራት ከተቀበለ በኋላም በ443 ዓ.ም. ከሮማ ፓፓና ከምሥራቅ አቡናዎች መካከል ልዩነት ደርሶባቸው፤ በ517 ሌላ መነኩሴ ዲዮኒሲዮስ ኤክሲጉዎስ ሌላ አቆጣጠር (አኖ ዶሚኒ) አቀረበ። በሱ ግምት ትስብዕቱ የተከሠተበት ቀን ከአኒያኖስ ግምት በፊት በ8 አመታት አስቀደመው። የአኖ ዶሚኒ አቆጣጠር በምዕራብ አውሮፓ ላይኛነት በማግኘቱ የትስብእት ዘመን 1 አመተ ምህረት በአኖ ዶሚኒ 9 እ.ኤ.አ ሆነ።

የኢትዮጵያ ዘመን ኣቆጣጠር የጁልያን ዘመን ኣቆጣጠር ኣይደለም።

[ለማስተካከል] ወራት

ዓማርኛ ጎርጎርዮስ በሰግር ዓመት
መስከረም ሰፕቴምበር 11 ሰፕቴምበር 12
ጥቅምት ኦክቶበር 11 ኦክቶበር 12
ኅዳር ኖቨምበር 10 ኖቨምበር 11
ታኅሣሥ ዲሰምበር 10 ዲሰምበር 11
ጥር ጃንዋሪ 9 ጃንዋሪ 10
የካቲት ፈብርዋሪ 8 ፈብርዋሪ 9
መጋቢት ማርች 10 ማርች 10
ሚያዝያ ኤፕሪል 9 ኤፕሪል 9
ግንቦት ሜይ 9 ሜይ 9
ሰኔ ጁን 8 ጁን 8
ሓምሌ ጁላይ 8 ጁላይ 8
ነሓሴ ኦገስት 7 ኦገስት 7
ጳጉሜን ሰፕቴምበር 6 ሰፕቴምበር 6

[ለማስተካከል] የውጭ መያያዣዎች