ከበደ ሚካኤል
ከWikipedia
ከበደ ሚካኤል (1907-1991) በአንኮበር ከተማ ተወለዱ። ወደ አዲስ አበባ እንደ መጡ መጀመሪያ በአሊአንስ ኢቲዮ-ፍራንሴዝ ብኋላም በላዛሪስት ሚሲዮን ትምህርታችውን ተከታተሉ። የሼክስፒርን ሮሜዎና ዡልየትን በመተርጎም እውቅናን ለማትረፍ ችለዋል።
ሌሎች ታዋቂ የትርጉም ሰራዎች ማሃል
- ከይቅርታ በላይ በሚል አርእስት ከBeyond the Pardon በ M.Clay የተተረጎመው ሊጠቀስ የቻላል።
ከበደ ሚካእል ካበረከቷችው የቴአትር ስራዎች
- የትንቢት ቀጠሮ
- የቅጣት ማእበል
- ካሌብ
- ሃኒባል
ይገኙባቸዋል።
ከበደ ሚካኤል በርካታ የስነ ጽሁፍ ስራዎች ባለቤት በመሆናችው በተለይም ለልጆች ትምህርት አዘል ጽሁፎችን የግጥም የፈጠራ ስራዎችን ቅኔዎችን በስፋት በማበርክታችው በኢትዮጵያ የስነጽሁፍ መድረክ ገናና ከሆኑት ደራሲዎች አንዱ ናችው። ከነዚህ መሃል
- ታሪክና ምሳሌ (፩ኛና ፪ኛ መጽሃፍት)
- የቅኔ ውበት
- የዕውቀት ብልጭታ
- ጃፓን እንዴት ስለጠነች
- ታላላቅ ሰዎች
ሊጠቀሱ ይችላሉ።
የሰዎች ስነ ምግባር ላይ የማተኮርና ምክር አዘል መልእክቶችን የማስተላለፍ ዝንባሌአችው በአብዛኛው ስራችው ላይ ይንጸባረቃል።