ዋርካ (ድረገጽ)

ከWikipedia

ዋርካ ከሳይበር ኢትዮጵያ የቀረበ የውይይት መድረክ ድረ ገጽ ነው። መልእክቶቹ በብዛት የተጻፉ በአማርኛ ስለሆነ ይህ ድረገጽ በተለይ ለኢትዮጵያውያን በፊደል ለመወያየት ይፈቅዳቸዋል። በሰኔ 1992 ተፈጥሮ ዛሬ ከሁሉ የተጠቀመው የአማርኛ ዌብሳይት ሆኖአል።

ካላፈው ግንቦት 1998 ጀምሮ ግን ሳይበር-ኢትዮጵያ እንደሚለው፥ የኢትዮጵያ መንግሥት በፖለቲካዊ ምክንያት ይህን ድረገጽ ስለአገደው በኢትዮጵያ ውስጥ ሊታይ አሁን አይቻልም። ሆኖም የመረጃ ሚኒስትር ብርሃኑ ሃይሉ ምንም ድረገጽ አልተከለከለምና የማይታዩበት ምክንያት አይታወቅም ብሏል። ዋርካ ወይም ሳይበር ኢትዮጵያ በምዕራቡ አለም ለሚኖረው ሕብረተሰብ በማህበራዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ወይም የዕለት ከዕለት ኑሮ መካከል ስለ ፖለቲካ ወይም ባሕል እና ስነ-ጽሑፍ፣ ስነ-ጥበብ ፤ ኪነ-ጥበብ ፤ ፍቅር ፡ሃይማኖት እንዲሁም ወቅታዊ ጉዳዮችን ሊያወያዩ የሚችሉ መድረኮች ስላሉት መፍትሔ ያጡለትን ጉዳይ ከኢትዮጵያውያን ጋር በመወያየት መፍትሔ እንደሚያገኙለት ከተጠቃሚዎች የተገኘ መረጃ ምስክር ነው ።

[ለማስተካከል] የውጭ መያያዣ