ጸጋዬ ገብረ መድህን
From Wikipedia
ጸጋዬ ገብረ መድህን (1928-1998) ባዳ ተብላ በምትታውቅ አምቦ ካተማ አካባቢ በምትገኝ ተራራማ ቦታ ተወለዱ። በአምቦ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከዚያም ዊንጌትና በአዲስ አበባ የንግድ ትምህርት ቤት በአገር ውስጥ ትምህርታችውን ከገፉ በኋላ በቺካጎ ብላክስቶን በህግ ትምህርት ተመርቀው በ1952 እንደ ውጡ በለንድን ከተማ የቴአትር ትምህርት በሮያል ኮርት ቴአትርና በፓሪስ ኮሜዲ ፍራንሴዝ ተከታትለዋል። ከ1954 እስከ 1964 የቤሄራዊ ቴአትር በአርቲስቲክ ዳይሬክተርነት አገለግለዋል። ከዚያም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቴአትር ዲፓርትመንትን አቋቁመዋል።
ሆኖም በ1960ዎቹ ደርግ አብዛኛውን የቴአትር ስራዎቻቸውን ሲያግድ እሳቸውንም ለማሰር በቅቷል።
ብላቴን ሎሬት ጸጋዬ በርካታ ግጥሞችን፥ የቴአትር ሰራዎችን የተለያዩ መጣጥፎችንና ዘፈኖችን አበርክታዋል። ጸጋዬ በ1990 ለጉበት በሽታ ሕክምና በመሻት ወደ ማንሃታን በሄዱበት አርፈዋል። በአዲስ አበባ በስላሴ ቤተክርቲያን ተቀብረዋል። ነፍሳቸውን በአብርሃም እቅፍ ያኑርልን::
ጨለማ ጽሕፈት